تحميل بصيغة PDF
العودة لقائمة القصص

ማጎዝዌ ماقزوي

كُتِب بواسطة Lesley Koyi

رسمة بواسطة Wiehan de Jager

بترجمة Dawit Girma

قرأه Abenezer Chane

لغة الأمهرية

مستوى المستوى 5

سرد للقصة كاملة

سرعة القراءة

تشغيل تلقائي للقصة


በተጨናነቀችው የናይሮቢ ከተማ በርካታ የጎዳና ተዳዳሪዎች ይኖራሉ። የስቃይ ኑሮ በየእለቱ ይገፋሉ፤ እያንዳንዱን ቀን አንዲሁ ይቀበሉታል። አንድ ቀን ጠዋት ልጆቹ ከመንገድ ዳር የተኙበትን ምንጣፍ ጠቀለሉ። ብርዱን ለመከላከል ቆሻሻ አንድደው እሳት ይሞቁ ነበር። ከልጆቹ ውስጥ ማጎዝዌ በእድሜ ትንሹ ነበር።

في مدينة نيروبي الصاخبة، بعيداً عن الحياة العائلية ودفئها، يعيش مجموعة من الصبيان بدون مأوى. كانوا يستقبلون كل يوم كما يأتي، لا أمل لهم فيه. وفي صباح أحد الأيام، أخذ الأطفال يحزمون حصائرهم بعد النوم على الأرصفة الباردة، ثم أشعلوا ناراً مما وجدوه من قمامة لمقاومة البرد. كان ماقزوي أحد هؤلاء الصبيان وكان أصغرهم سناً.


ወላጆቹ ሲሞቱ ማጎዝዌ ገና 5 ዓመቱ ነበር። ከአጎቱ ጋር ለመኖር ሄደ። አጎትዬው ግን ለልጁ አያስብለትም ነበር። ለማጎዝዌ በቂ ምግብ አይሰጠውም። ከባባድ ስራዎች ያሰራው ነበር።

كان ماقزوي يبلغ من العمر خمس سنوات عندما توفي والداه، فانتقل للعيش مع خاله. لكن هذا الرجل لم يكترث بالطفل ولم يوفر له القدر الكافي من الطعام كما كان يجبره على القيام بأعمال شاقة.


ማጎዝዌ ካማረረ ወይ ጥያቄ ከጠየቀ አጎቱ ይገርፈዋል። ትምህርት ቤት ለመሄድ ሲጠይቅ አጎቱ ይመታውና እንዲህ ይላል፣ ‹‹አንተ በጣም ደደብ ነህ ምንም መማር አትችልም›› በእንዲህ አይነት ሁኔታ ሶስት ዓመታት ከቆዬ በኋላ አንድ ቀን ሮጦ ከአጎቱ አመለጠ። ጎዳና መኖርም ጀመረ።

وكان أيضاً يضربه كلما استفسر ماقزوي عن أمر أو تذمر من كثرة العمل. وعندما طلب ماقزوي من خاله أن يسمح له بالذهاب إلى المدرسة ضربه من جديد قائلا: “أنت غبي جدا ولن تتعلم أي شيء”. وبعد ثلاث سنوات من هذه المعاملة القاسية، هرب ماقزوي من خاله وبدأ يعيش في الشارع.


የጎዳና ህይወት በጣም አስቸጋሪ ሲሆን ልጆች ምግብ ለማግኘት በየቀኑ ሲለፉ ይውላሉ። አንዳንዴ ይታሰራሉ፣ አንዳንዴ ደግሞ ይገረፋሉ። ሲታመሙ የሚያሳክማቸው ማንም የለም። ልጆቹ ኑሯቸውን የሚገፉት በልመና እና የወዳደቁ እንደላስቲክ አይነት ነገሮችን በመሸጥ በሚያገኙት ትንሽ ገንዘብ ነው። ከከተማው ሌላ ሰፈር ካሉ ሌሎች ጎዳና ተዳዳሪዎች ጋር የተሻለ ለማግኘት የሚያደርጉት ፉክክር ኑሯቸውን ይበልጥ ያመረዋል።

كانت الحياة في الشارع صعبة وكان أغلب الأطفال يعانون يومياً من أجل لقمة العيش. فكانت الشرطة تلقي عليهم القبض أحياناً، وأحياناً أخرى كانوا يتعرضون للضرب. وكانوا إذا ما مرضوا لا يجدون من يقدم لهم يد المساعدة. كانت مجموعة الأطفال تعتمد على النزر القليل من المال الذي كانوا يحصلون عليه من التسول ومن بيع البلاستيك ومواد أخرى مما تقع إعادة تدويره. كانت الحياة تزداد صعوبة خاصة بسبب المعارك التي تحدث بين جماعات الأطفال المتنافسة من أجل السيطرة على أحياء المدينة.


አንድ ቀን ማጎዝዌ የቆሻሻ ገንዳ ላይ እየፈለገ ሳለ አንድ የሆነ የተጎሳቀለና ያረጀ የተረት መጽሐፍ አገኘ። አጸዳዳውና በቦርሳው ከተተው። በየቀኑ መጽሐፉን ያወጣና ስእሎቹን ያያል። ማንበብ ግን አይችልም ነበር።

وفي يوم من الأيام، بينما كان ماقزوي يبحث في صناديق القمامة عن شيء يأكله، إذ به يجد مجموعة قصص رثة ممزقة. قام ماقزوي بتنظيف القصص من الأوساخ ووضعها في جرابه. وكان كل يوم يخرج الكتاب من كيسه وينظر إلى الصور، إذ لم يكن ماقزوي يعرف قراءة الكلمات.


ስእሎቹ ስለአንድ አውሮፕላን አብራሪ መሆንን እየተመኘ ስላደገ ልጅ ይተርካል። ማጎዝዌ አውሮፕላን አብራሪ የመሆን ነገር እንደቅዠት ያልም ጀመር። በተረቱ ውስጥ ያለው ልጅ ታሪክ የእሱ ይመስለዋል።

كانت الصور تحكي قصة طفل نشأ ليكون طياراً. أصبح ماقزوي يمضي يومه حالماً بأن يكون طياراً، وكان من حين لآخر يرى نفسه مكان ذاك الولد الذي تصفه الصور.


ቀዝቃዛ ነበር፤ ማጎዝዌም መንገድ ዳር ቆሞ ይለምናል። አንድ ሰው ወደእሱ እየተራመደ ሄደ። ‹‹ሰላም! ቶማስ እባላለሁ፣ እዚሁ አካባቢ ነው የምሰራው፣ አንተ ምግብ ማግኘት የምትችልበት ቦታ›› አለ ሰውየው። ቢጫ ቀለም ወደተቀባ ባለ ሰማያዊ ጣራ ቤት ጠቆመ። ‹‹ርግጠኛ ነኝ ወደዚያ ሄደህ ምግብ ትለምናለህ?›› ሰውየው ጠየቀ። ማጎዝዌ አንዴ ሰውየውን ቀጥሎ ደግሞ ቤቱን ተመለከተ። ‹‹ምናልባት›› አለ፤ ከዚያም ሄደ።

كان الجو بارداً وكان ماقزوي يقف متسولاً في الطريق عندما تقدم إليه رجل قائلا: “أهلاً… أنا توماس. أعمل قريباً من هنا، في مكان يمكن أن تجد فيه شيئاً تأكله”. وأشار بإصبعه إلى منزل أصفر ذي سقف أزرق، وسأل ماقزوي: “ألا ترغب في الذهاب إلى هناك لتناول بعض الطعام؟”. نظر ماقزوي إلى الرجل ثم إلى المنزل وقال: “ربما” وانصرف بعيداً.


በቀጣዮቹ ወራት ጎዳና ተዳዳሪዎቹ ልጆች ቶማስን በአካባቢው መመልከት ለመዱ። ቶማስ ከሰዎች ጋር ማውራት ይወዳል በተለይ ከጎዳና ተዳዳሪዎች ጋር። ቶማስ የሰዎችን ታሪክና የህይወት ገጠመኝ ያዳምጣል። ቆፍጣናና ትእግስተኛ ነው፤ ትእቢተኛና ሰው የማያከብር አይደለም። አንዳንዶቹ ልጆች ወደ ቢጫና ሰማያዊው ቤት ምግብ ለማግኘት በእኩለ ቀን መሄድ ጀመሩ።

توالت الأشهر بعد ذلك، وتعود الأولاد المشردون على رؤية توماس يرتاد المكان الذي يتواجدون فيه. كان يحب الحديث إلى الناس، وخاصة من كانوا يعيشون في الشوارع. كان يستمع إلى قصص حياتهم. وكان جدياً، صبوراً، ولم يكن قاسياً أبداً ولا قليل الاحترام لهم. بدأ بعض الصبيان يترددون على المنزل ذي اللونين الأصفر والأزرق للحصول على ما يسد رمقهم عند منتصف النهار.


ማጎዝዌ መንገዱ ዳር እግረኛ መንገድ ጥግ ሆኖ ባለስእል የተረት መጽሐፉን እየተመለከተ ሳለ ቶማስ መጥቶ አጠገቡ ተቀመጠ ። ‹‹ተረቱ ስለምንድን ነው?›› ቶማስ ጠየቀ። ‹‹አንድ ፓይለት ስለሆነ ልጅ ታሪክ ነው›› መለሰ ማጎዝዌ። ‹‹የልጁ ስም ማነው?›› ጠየቀ ቶማስ። ‹‹አላውቅም፤ ማንበብ አልችልም እኮ›› አለ ማጎዝዌ ለስለስ ብሎ።

كان ماقزوي يوما ما جالساً على الرصيف يتأمل كتاب الصور عندما جلس توماس لجانبه وسأله: “عما تحكي هذه القصة؟”. أجاب ماقزوي: “عن ولد أصبح طياراً”. قال توماس: “ما اسم هذا الولد؟” أجاب ماقزوي بهدوء: “لا أعرف. لا أستطيع القراءة”.


በተገናኙ ጊዜ ማጎዝዌ ታሪኩን ሁሉ ለቶማስ ያጫውተዋል። አጎቱ እንዴት እንዳደረገው እና እንዴት ማምለጥ እንደቻለ ይነግረዋል። ቶማስ ብዙ አያወራም፣ ማጎዝዌንም እንዲህ አድርግ እንዲያ አታድርግ አይልም፣ ዝም ብሎ በአትኩሮት ብዙ ያዳምጠዋል። አንዳንዴ ባለሰማያዊው ጣራ ትልቁ ቤት ምግብ ሲበሉም ያወራሉ።

عندما تقابلا، بدأ ماقزوي يسرد قصته على توماس، قصته مع خاله وكيف هرب منه. لم يتكلم توماس كثيرا، ولم يُمْلِ على ماقزوي ما يجب عليه فعله، لكنه كان يصغي إليه بانتباه طوال الوقت. وكانا أحياناً يواصلان حديثهما بينما يتناولان الطعام في المنزل ذي السقف الأزرق.


የማጎዝዌ 10ኛ ዓመት ልደት ሲደርስ ቶማስ ለማጎዝዌ አዲስ የተረት መጽሐፍ ሰጠው። ዝነኛ እግር ኳስ ተጫዋች ስለሆነ በአንድ መንደር ይኖር ስለነበረ ልጅ ነበር ታሪኩ የሚያትተው። ቶማስ ይህን ታሪክ ለማጎዝዌ ብዙ ጊዜ አነበበለት፤ አንድ ቀን እንዲህ አለው፣ ‹‹እንደማስበው አሁን ትምህርት ቤት የምትገባበትና ማንበብ የምትማርበት ጊዜ ነው። ምን ታስባለህ?›› ቶማስ የልጆች ማቆያና ትምህርት ማግኘት የሚችሉበት ቦታ መኖሩን አብራራለት።

وبحلول عيد ميلاد ماقزوي العاشر، أهداه توماس قصةً جديدةً. كانت القصة تحكي عن ولد نشأ في قرية ليصبح بعد ذلك لاعب كرة قدم مشهور. قرأ توماس القصة مرات عديدة لماقزوي، ثم قال له في أحد الأيام: “أظن أن الوقت قد حان لتذهب إلى المدرسة وتتعلم القراءة، ما رأيك؟” وأوضح له بأنه يعرف مكانا يمكن لأطفال الشوارع أن يقيموا فيه ويرتادوا المدرسة.


ማጎዝዌ ስለተጠቆመው አዲስ ቦታና ትምህርት ማግኘት ስለሚችልበት ሁኔታ ማሰላሰል ያዘ። አጎቱ ያለው ትክክል ቢሆንስ? ትምህርት መማር የማይችል በጣም ደደብ ቢሆንስ? እዚህ አዲስ ቦታ ከሄደ በኋላ ቢገርፉትስ? መፍራት ጀመረ። ‹‹ምናልባትም እዚሁ ጎዳና ላይ መሆን ሳይሻል አይቀርም›› ብሎ አሰበ።

فكر ماقزوي في هذا المكان الجديد وفي الذهاب إلى المدرسة وتساءل: “ماذا لو كان خاله على حق حينما نعته بالغبي؟ لن يستطيع تعلم أي شيء عند ذلك. ماذا لو قاموا بضربه في ذاك المكان الجديد؟” شعر ماقزوي بالخوف وقال محدثا نفسه: “قد يكون من الأفضل لي مواصلة العيش في الشارع”.


ስጋቱን ለቶማስ አጋራው። ከጊዜ በኋላ ቦታው ትክክለኛና የተሻለ መሆኑን ቶማስ አረጋገጠለት።

أعلم ماقزوي توماس بمخاوفه. وبمرور الوقت طمأن توماس الصبي بأن الحياة قد تكون أفضل في المكان الجديد.


ከዚያም ማጎዝዌ ባለአረንጓዴ ጣራ ቤት ውስጥ ወዳለ አንድ ክፍል ሄደ። ክፍሉን ከሌሎች ሁለት ልጆች ጋር ነው የተጋራው። በቤቱ ባጠቃላይ አስር ልጆች ይኖራሉ። አብረውም ሲሲ እና ባሏ፣ ሶስት ውሻዎች፣ አንዲት ድመት እንዲሁም አንድ ያረጀ ፍየል ይኖራሉ።

لذا انتقل ماقزوي للعيش بغرفة في منزل ذي سقف أخضر. تقاسم الغرفة مع صبيين آخرين. كان المنزل يضم عشرة أولاد إلى جانب العمة سيسي وزوجها وثلاثة كلاب وقطة وعنزة عجوز.


ማጎዝዌ ትምህርት ጀመረ፣ ግን ትምህርቱ ትንሽ አስቸጋሪ ሆኖበታል። አንዳንዴ ለማቋረጥ ሁሉ ይመኛል። ነገር ግን አየር አብራሪ እና ታዋቂ ኳስ ተጫዋች የሆኑትን በተረቱ ውስጥ ያሉትን ልጆች ያስባል። ልክ እንደነሱ ትምህርቱን ማቋረጥ የለበትም፣ እነሱ እንደሆኑት ሁሉ ያሰበበት መድረስ ይችላል።

بدأ ماقزوي الدراسة. كانت صعبة في البدء، وكان عليه أن يعمل جاهداً لتدارك ضعفه. مرت عليه لحظات يأس أراد فيها أن يغادر المكان لكنه كان في كل مرة يتذكر قائد الطائرة ولاعب كرة القدم اللذين تحكي عنهما القصص، وعقد العزم على ألا يغادر المدرسة وأن يواصل تعليمه.


ባለአረንጓዴ ጣራው ቤት ግቢ ውስጥ ቁጭ ብሎ ከትምህርት ቤት የወሰደውን የተረት መጽሐፍ ያነባል። ቶማስ መጣና አጠገቡ ተቀመጠ። ‹‹ተረቱ ስለምን ነው?›› ቶማስ ጠየቀ። ‹‹ታሪኩ አንድ መምህር ስለሆነ ልጅ ነው።›› ማጎዝዌ መለሰ። ‹‹የልጁ ስም ማነው?›› ጠየቀ ቶማስ። ‹‹ስሙ ማጎዝዌ ይባላል!›› አለ ማጎዝዌ በፈገግታ።

وفي يوم من الأيام، كان ماقزوي جالسا في فناء المنزل ذي السقف الأخضر يقرأ قصة من المدرسة عندما أقبل توماس وجلس لجانبه سائلا: “عما تتحدث القصة؟” رد ماقزوي قائلا: “إنها تحكي عن صبي أصبح مدرسا” سأل توماس: “ما اسم هذا الصبي؟” أجاب ماقروي مبتسما: “اسمه ماقزوي”.


كُتِب بواسطة: Lesley Koyi
رسمة بواسطة: Wiehan de Jager
بترجمة: Dawit Girma
قرأه: Abenezer Chane
لغة: الأمهرية
مستوى: المستوى 5
المصدر: Magozwe از القصص الأفريقية القصيرة
رخصة المشاع الإبداعي
تحت مجوز المشاع الإبداعي نَسب المُصنَّف 4.0 دولي کریتز کامنز به نشر رسید.
بیشتر بخوانید سطح 5 داستان ها:
خيارات
العودة لقائمة القصص تحميل بصيغة PDF